ህብረተሰቡን ወደ ቴክኖሎጂው እናደርሳለን


በይነመረብ የኢንተርኔት አጠቃቀም መመሪያ በአማርኛ የተባለው መጽሐፍ ተጽፎ ለህዝብ አገልግሎት ጥቅም ላይ ከዋለ ቦኃላ ትንሽ የማይባሉ የመጽሐፉ አንባቢዎች የቴክኖሎጂውን አጠቃቀም በተመለከተ የቤት ለቤት ስልጠና እንድንሰጣቸው ጠይቀውናል፡፡
  1. ቴክኖሎጂውን የመጠቀም ጉጉቱ ኑሯቸው ትምህርት ቤት ገብቶ ለመማር ግዜውን ያጡ፡፡ታዋቂ ሰዎች ሆነው የቴክኖሎጂውን ውስጣዊ አሰራር የበለጠ ለመረዳት ግዜ ያጠራቸው፡
  2. እንደማንኛውም መደበኛ ትምህርት የራሱ ክፍለ ግዜ የሌለው ሰለሆነ በኢንትርኔት አጠቃቀሙ ዙሪያ በቂ እውቀት ያልጨበጡ፡
  3.  እንደማንኛውም የቴክኖሎጂ ሰው ክፍለ ዘመኑን በብልጥት እና በእውቀት ለመቆጣጠር የሚፈልጉ፡
  4. የድርጅቶቻቸውን እና የንግዶቻቸውን አሰራር ከቴክኖሎጂው ጋር ለማዋደድ የሚሹ፡
  5. ልጆቻቸው ሰለ እንተርኔት አጠቃቀም በሚገባ ማወቃቸው በትምህርታቸው ሆነ በስነምግባራቸው ላይ ለውጥ ያመጣል ብለው የተገነዘቡ ታዋቂ ሰዎች፣ ነጋዴዎች፣ ግለሰቦች፣ ተማሪዎች፣ ድርጅቶች፣ ወዘተ ስማቸውን እና አድራሻችውን ጠቅሰው በስልክ እና ኢሜይል አድራሻችን የተለያዩ መልእክቶችን አስተላለፈውልናል፡ ከዚህ በመነሳት ጉዳዩን ስናስብበት ከቆየን ቦኃላ እንደየአስፈላጊነቱ ለተግባራዊነቱ እቅድ አውጥተን እንቅስቃሴ ጀምረናል እርስዎም የእቅዱ ተጠቃሚ እንዲሆኑ እንጋብዛለን፡፡ ይደውሉልን 0912153087  

No comments: